አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አዲስ የሚደገፉ ኢንተርፕራይዞች ርክክብና የአንቀሳቃሾች የስራ ፈጠራና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠና ሰጠ
ህዳር 23፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ - አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ አዲስ የሚደገፉ ኢንተርፕራይዞች ርክክብና የአንቀሳቃሾች የስራ ፈጠራና የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠና የሰጠ ሲሆን፤
ይህ ተግባር ኮሌጁ የኢንዳስትሪ ኤክስቴንሽን አገልግሎት የሚሰጣቸው አዲስ ኢንተርፕራይዞችና አንቀሳቃሾቻቸው ከአራቱ ድጋፍ ማዕቀፎች ውስጥ የሂሳብ መዝገብ አያያዝ ስልጠናዎችን እንዲያገኙና በብሄራዊ ምዘና በማለፍ እንዲበቁ የሚደረግበት ስርዓት እንደሆነ ተመላክቷል፡፡
ስልጠናው አዲስ የሚደገፉ ኢንተርፕራይዞች ውጤታማ ሂሳብ መዝገብ አያያዝና መሰረታዊ የስራፈጠራ ክህሎቶችን እንዲያዳብሩ በማድረግ የንግድ ስራ እቅድ፣ የፋይናንስ አስተዳደር፣ የግብይት ስልቶች ከስራ ፈጣሪነት ቁልፍ ገጽታዎች ጋር የሚያስተዋውቃቸው ነው፡፡
<<ከፋታን ማጽናት፣ነገን ማላቅ>>

.