አራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የብሄር ብሄረሰቦች ቀንን አከበረ
አዲስ አበባ፣ ህዳር 11፣ 2018፤ የአራዳ ማኑፋክቸሪንግ ኮሌጅ የማህበረሰብ አባላት የብሔር ብሄረሰብ ቀንን “ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለህብረ ብሔራዊ መግባባት” በሚል መሪቃል አክብረዋል፡፡
የበዓሉን አከባበር መሰረት በማድረግ “ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለህብረ ብሔራዊ መግባባት” በሚል መሪቃል የመወያያ ሰነድ የቀረበ ሲሆን የመወያያ ሰነዱን መነሻ በማድረግ ተሳታፊዎች የተለያዩ ሀሳቦችና ጥያቄዎችን በማንሳት ተወያይተዋል፡፡
የኮሌጁ አዋሬ ካምፓስ ምክትል ዲን አቶ ተፈሪ ንጉሴ እንዳብራሩት "በአላችን ባህልን ማሳየት ብቻ ሳይሆን ትርጉም ያለው ውይይት በማድረግ መግባባትን የሚያጎለብት እና ማህበረሰቡን አብሮነት የሚያጠናክር መሆን እንዳለበት አጽንኦት ሰተዋል"፡፡
“ዴሞክራሲያዊ አንድነት ለህብረ ብሔራዊ መግባባት”
<<ከፍታን ማፅናት፤ ነገን ማላቅ>>
.